Thesis Open Access
በአብዮት አራጋው
በኢዮብ ቀለመወርቅ (ዶ/ር)
አጠቃሎ የዚህ ጥናት አብይ ዓላማ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል የ3ኛ ክፍል አማርኛ እንደ አፍመፍቻ ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት ግምገማ ነው፡፡ በመሆኑም የመማሪያ መጽሐፉ የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት በስፋትና በጥልቀት ተፈትሸዋል፡፡ የጥናቱን ዓላማ ለማሳካት ወሳኝ የናሙና ዘዴ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ ጥናቱም ዓላማ ተኮር የናሙና አመራረጥ ስልትን ተጠቅሟል፡፡ ጥናቱ በሰነድ ፍተሻ መረጃዎችን ሰብስቧል፡፡በሰነድ ፍተሻ የመረጃ መሰብሰቢያ የተሰበሰቡ መረጃዎችን በዓይነታዊ ስልት በመጠቀም ተተንትኗል፡፡ ማብራሪያም ተደርጎባቸዋል፡፡ የጥናቱ ግኝትም በመማሪያ መጽሐፉ የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት ካነሳቸው የይዘት አደረጃጀትና አቀራረብ አንጻር ተከታታይነትና ተለጣጣቂነት ጥሩ በሚባል አደረጃጀት እንደቀረቡ ተረጋግጣል፡፡ ዘጠና ሰባት በመቶ የሚሆነው የሰዋስው ይዘት ከአቀራረብ፣ ከተገቢት፣ ከግልጸኝነት፣ ከትክክለኛነት እና ከተመጣጣኝነት አንጻር እንደ ጠንካራ ጎን የታየ ሲሆን በመማሪያ መጽሐፉና ለደረጃው የተዘጋጀው መርሀ ትምህርት ግን በምዕራፍና በጊዜ አለመከፋፈሉ እንደ ድክመት ታይቷል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግም በጥናቱ መጨረሻ ላይ ክፍተቱን ለመሙላት የሚያስችሉ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡
| Name | Size | |
|---|---|---|
|
5. Abiyot Aragaw resrearch 1.pdf
md5:41f48e9f77604b7fc1074454fb8cb817 |
707.2 kB | Download |
| All versions | This version | |
|---|---|---|
| Views | 0 | 0 |
| Downloads | 0 | 0 |
| Data volume | 0 Bytes | 0 Bytes |
| Unique views | 0 | 0 |
| Unique downloads | 0 | 0 |