Thesis Open Access

በ2007 የተዘጋጁ የሰባተኛ እና ስምንተኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻህፍት የሰዋስው ይዘት አመራረጥ እና አደረጃጀት ፍ

ካሳሁን ኩራባቸው

Thesis supervisor(s)

ኢዮብ ቀለመወርቅ (ዶ/ር)

ይህ ጥናት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የትምህርት ሚኒስቴር በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ተዘጋጅቶ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ የተስማማ አማርኛን እንደ አፍ መፍቻ ቋንቋ የተማሪ መጽሐፍ የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ላይ የተካሔደ ጥናት ነው፡፡ የጥናቱ ዋነኛ ትኩረት በ2007 የተዘጋጁ የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋመማሪያመጻህፍት የሰዋስው ይዘት አመራረጥ እና አደረጃጀት መገምገም የጥናቱ አብይ ስራ ነው፡፡ ይህን የጥናቱን አብይ ትኩረት መነሻ በማድረግ በታላሚዎቹ የክፍል ደረጃ ላይ የሚገኙት መጽሐፍ በጥልቀት በመፈተሸ የታላሚዎቹን መጽሐፍ የሰዋስው ይዘቶች አመራረጣቸውን እና አደረጃጀታቸውን በምን መልኩ እንደተደራጁ እንዲሁም የመጽሐፉን ጠንካራ እና ደካማ ጎናቸውን መፈተሽ የዚህ ጥናት ዋነኛው መዳረሻ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በየመማሪያው መጽሐፍ ውስጥ የቀረበ የሰዋስው ይዘቶችም ከአመራረጥ ከትክክለኛነት፣ ከግልጽነት፣ ከተመጣጣኝነት እና ከተገቢነት አንፃር አደረጃጀትን በተመለከተ ተከታታይነት እና ተለጣጣቂነትን እንዲሁም አወቃቀርን በተመለከተ ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ እና የሁለቱንም ስብጥራዊ አጠቃቀም ገጽታ ለማየት ተሞክሯል፡፡ በዚህ ጥናት በመማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የቀረቡ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አመራረጥ እና አደረጃጀት በምዕራፍ ሁለት ከቀረቡት ፅንስ ሃሳባዊ መርሆች አንፃር በማየት ተተንትነዋል፡፡ በዚህ መሰረት በታላሚ የመማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ይዘቶች ላይ መጠነኛ የአመራረጥ እና የአደረጃጀት ችግሮች መታየታቸውን በሰነድ ፍተሻው ተረጋግጧል፡፡ በመጨረሻም በዚህ ጥናት ውስጥ የሰዋስው ትምህርት አመራረጥ እና አደረጃጀት ላይ የታዩ ድክመቶችን ለማረም ያስችላሉ የተባሉ አስተያየቶችን በአጥኚው እንደ መፍትሔ ሃሳብነት ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡ ይኸውም በመማሪያ መጽሐፍ ውስጥ በተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች ላይ የታዩትን የአመራረጥ እና የአደረጃጀት ችግሮችን ለማስወገድ ትኩረት መስጠት በመማሪያ መጽሐፍ ዝግጅት ወቅት ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ባለሙያዎች አስተያየት እንዲሰጡ እድሉን ማመቻቸት፣ ምጋቤ መልሶችንም ተግባራዊ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

Files (700.7 kB)
Name Size
14. Kasu K. Final Research.pdf
md5:feecac843756b00079508c85cca67f9f
700.7 kB Download
0
0
views
downloads
All versions This version
Views 00
Downloads 00
Data volume 0 Bytes0 Bytes
Unique views 00
Unique downloads 00

Share

Cite as